Thursday, October 31, 2013

የኢትዮጲያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግንባር መፍጠር
10 ያህል የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ይበልጥ ተባብረው በጋራ ለመታገል ያስችላቸው ዘንድ የጋራ ግንባር መፍጠራቸውን ኣስታወቁ።
እነዚሁ ቀደም ሲል 33ቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ይባል የነበረው ስብስብ አካል የነበሩ 10 ፓርቲዎች የፈጠሩት ጥምረት ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ወይንም በአጭሩ ትብብር ተብሎ ይጠራል ተብለዋል።
አዲሱ ትብብር ከምርጫ ቦርድም የምዝገባ ማረጋገጫ ማግኝቱ ታውቀዋል
ሰላሳ ሶስቱ ፓርቲዎች እየተባሉ የሚጠሩት ጥቅምት 15 ቀን 2005 ዓ ም በምርጫ ጉዳይ ላይ የአዳማውን ፒቲሺን የፈረሙ ፓርቲዎች ናቸው። ከእነዚሁ መካከል የመግባቢያ ሰነዱን የፈረሙት ግን 24 ፓርቲዎች ሲሆኑ ካለፈው ጥቅምት 10 ቀን ወዲህ ደግሞ ወደ ቅንጅት ኣድገው ነበር።
ባለፈው እሁድ በተካሔደው የጋራ ጉባዔ ላይ ደግሞ 10 ፓርቲዎች የመመስረቻ ጽሁፍ የመተዳደሪያ ደንብ እና መለስተኛ የድርጊት ፕሮግራም በመፈረም አቶ አለሳ መንገሻ የጌድኦ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ሊቀመንበር እና የአዲሱ ትብብር ኣስተባባሪ ኮሚቴ እንዳስረዱት ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ወይንም በአጭሩ ትብብር በሚል መጠሪያ መቀናጀታቸውን ኣውጀዋል።
በእርግጥ የመድረክ አባል ድርጅቶች ለመቀናጀት ቴክኒካዊ ችግሮች ስላሉባቸው እንጂ ለመተባበር ዝግጁ መሆናቸውም ተጠቅሰዋል። መድረክ ውስጥ ያለው ቴክኒካዊ ችግር ደግሞ አቶ አለሳ እንደሚሉት መድረክ ግንባር በመሆኑ በመተዳደሪያ ደንባቸው መሰረት ኣንድ የመድረክ አባል ድርጅት ከሌሎች ድርጅቶች ጋር መዋሀድ እንጅ በትብብር ደረጃ መቀናጀት ስለማይችል ነው ተብለዋል። የመድረክ አባል ድርጅቶች የውስጥ ችግራቸውን ከፈቱ በአዲሱ ትብብር በኩል አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም አቶ አለሳ ኣስምረውበታል።
የመድረክ አባል ድርጅቶችን ሳይጨምር በአዲሱ ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ውስጥ ካልተካተቱት መካከልም ስማያዊ ፓርቲን ጨምሮ የሲዳማ ህዝብ ዓርነት ንቅናቄ እና የጉራጌ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ይገኙበታል።
ኣሁን ትብብር ፈጥረው እስከ መዋሀድ ልንሄድ እንችላለን የሚሉት ፓርቲዎች ኣንዳንዶቹ ኣገራዊ ፓርቲዎች ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ ብሔራዊ ፓርቲዎች ናቸው። ይህንኑ ጉዳይ በማንሳት የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በኣንድ ወቅት እሳት እና ውሃ እንዴት አብሮ ለመስራት እንደሚስማሙ ኣይገባኝም ማለታቸው የሚታወስ ሲሆን አቶ አለሳ ግን በዚህ ኣይስማሙም።
ምንም እንኩዋን የመጫወቻው ሜዳ ችግር እንዳለበት ቢገባንም በህገ መንግስቱ ድንጋጌዎች ላይ ከኢህኣዲግ ጋር ልዩነት የለንም የሚሉት አቶ አለሳ መንግስት ህገ መንግስቱን እንዲያከብር ተስፋ ሳንቆርጥ እና ሳንታክት ታግለን ህዝባችንን ኣንቀሳቅሰን ለውጥ ለማምጣት እንሰራለን ብለዋል።
የስደት መንስኤ ፖለቲካዊ ጉዳይ ሆኖ እያለ መንግስት ግን ችግሩን ወደ ደላላ 
መንግስት ስደትን ለመቆጣጠር በሚል ለደላላዎች አዋጅ እንዳወጣው ሁሉ ለአገራችን ምስቅልቅልና የስደት ምንጭ ደላላ የሆነው ራሱን የሚገድብ አዋጅ ያስፈልገዋል፡፡ ስልጣን በአዋጅ (በህግ) እስካልተገደበና መረን እስካልያዘ ድረስ ኢትዮጵያውያን ይሰደዳሉ፡፡ ካድሬዎችም ቢሆን!
ስደትን በጊዜያዊ አዋጅ?

ኢትዮጵያዊያን በግል ሳይሆን በመንጋ የተወለዱበትን ቀዬ ትተው ወደማያውቁት ምድር እየጎረፉ ነው፡፡ ይባስ ብሎ ካሰቡት ሳይደርሱ በየ በርሃውና ባህሩ እየቀሩ ነው፡፡ ይህን የኢትዮጵያውያን እጣ ፈንታ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በሰፊው መዘገባቸውን ተከትሎ መንግስትም ‹‹መፍትሄ›› የሚለውን አስቀምጧል፡፡ ኢትዮጵያውያን የሚሰደዱት በአመለካከት ችግር መሆኑን የሚያምነው መንግስት በጊዜያዊ አዋጅ ስደትን ለመከላከል እየሞከረ ነው፡፡

ኢትዮጵያ የገዥዎች እንጅ የዜጎቿ ሆና አታውቅም፡፡ ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ደግሞ ይህ ባይተዋርነት ሌላ መልክን ይዟል፡፡ ተራ ዜጋ ብቻ ሳይሆን ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ ሙዚቀኞች፣ ጀኔራሎችም እግሬን አውጭኝ ብለው ከአገር እየተሰደዱ ነው፡፡ መንግስት ይህኛውን ሳይሆን በሱዳን፣ ኬንያና ሶማሊያ የሚፈልሱትን ነው ለማቆም እጥራለሁ የሚለን፡፡ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ ጀኔራሎች የሚሰደዱበትን አብሮ ማንሳት ፖለቲካዊ ቃና ስለሚይዝ ማንሳት አልፈለገም፡፡ 
እርግጥ ነው ወንድምና እህቶቻችን ኮንተይነር ውስጥ መሞታቸው ልብ የሚነካ ነው፡፡ የአሳ ራት፣ የበርሃ ሲሳይ ሲሆኑም እጅጉን ያስቆጫል፡፡ በማያውቁት አገር ፖሊስ ሲገረፉ፣ ሲደፈሩና ሲንገላቱ መስማት ያሳምማል፡፡ መፍትሄም ያስፈልገዋል፡፡ ግን ግን ማዕከላዊ (የኢትዮጵያዊ ጓንታናሞ)፣ የቀጨኔው ወረዳ ዘጠኝ፣ ዝዋይ ታጉረው የሚገረፉት፣ የሚሰቃዩት ዜጎች በስደት ከሚሰቃዩት በምን ይሻላሉ? ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት ሰባት፣ ተቃዋሚ፣አክራሪ…… እየተባሉ የሚገረፉት፣ ከስራ የሚባረሩት የተወለዱበትን አገር ጥለው ሲጠፉ ተጠያቂው ማን ነው? ለምን ለዚህኛው ባይተዋርነትስ አወጅ አይወጣለትም?

የአገራችን ዋነኛው የስደት መንስኤ ፖለቲካዊ ጉዳይ ሆኖ እያለ መንግስት ግን ችግሩን ወደ ደላላ ዝቅ አድርጎታል፡፡ እውነቱን ለመናገር ለኢትዮጵያውያን የስደት ስቃይ መጠየቅ ካለበት ለፖለቲካ ምስቅልቅሉ መንስኤ የሆነው መንግስት ራሱ ነው፡፡

እውቅ ጋዜጠኞች፣ ምሁራን፣ ፖለቲከኞች፣ ጀኔራሎች ወደ ውጭ የሚሰደዱት የቀን ስራ ለመስራት ሳይሆን ልክ ወደ አረብ አገር የሚሰደዴት እህቶቻችን የመን ላይ እንደሚገጥማቸው እስራትና ግርፋት እትብታቸው በተቀበረበት ምድር ስቃዩ ስለበዛባቸው ነው፡፡ አሁንም ቢሆን ስፍር ቁጥር የሌላቸው ዜጎች የዚህ ስቃይ ሰለባዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ወገኖች መውጫ ቀዳዳውን ካገኙ አሁንም ይሰደዳሉ፡፡ ለአንድ ማህበረሰብ ቁልፍ የሆኑት ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች፣ ሙዚቀኞች… በፖለቲካ ችግር ከተሰደዱ ተራው ዜጋም የትውልድ አገሩን የነጠቁትን ሽሽት መጉረፉን ይቀጥላል፡፡ እኛ አገርም እየሆነ የሚገኘው ይኸው ነው፡፡
የስደት መንስኤ ፖለቲካዊ ጉዳይ ሆኖ እያለ መንግስት ግን ችግሩን ወደ ደላላ 
መንግስት ስደትን ለመቆጣጠር በሚል ለደላላዎች አዋጅ እንዳወጣው ሁሉ ለአገራችን ምስቅልቅልና የስደት ምንጭ ደላላ የሆነው ራሱን የሚገድብ አዋጅ ያስፈልገዋል፡፡ ስልጣን በአዋጅ (በህግ) እስካልተገደበና መረን እስካልያዘ ድረስ ኢትዮጵያውያን ይሰደዳሉ፡፡ ካድሬዎችም ቢሆን!
ስደትን በጊዜያዊ አዋጅ?

ኢትዮጵያዊያን በግል ሳይሆን በመንጋ የተወለዱበትን ቀዬ ትተው ወደማያውቁት ምድር እየጎረፉ ነው፡፡ ይባስ ብሎ ካሰቡት ሳይደርሱ በየ በርሃውና ባህሩ እየቀሩ ነው፡፡ ይህን የኢትዮጵያውያን እጣ ፈንታ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በሰፊው መዘገባቸውን ተከትሎ መንግስትም ‹‹መፍትሄ›› የሚለውን አስቀምጧል፡፡ ኢትዮጵያውያን የሚሰደዱት በአመለካከት ችግር መሆኑን የሚያምነው መንግስት በጊዜያዊ አዋጅ ስደትን ለመከላከል እየሞከረ ነው፡፡

ኢትዮጵያ የገዥዎች እንጅ የዜጎቿ ሆና አታውቅም፡፡ ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ደግሞ ይህ ባይተዋርነት ሌላ መልክን ይዟል፡፡ ተራ ዜጋ ብቻ ሳይሆን ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ ሙዚቀኞች፣ ጀኔራሎችም እግሬን አውጭኝ ብለው ከአገር እየተሰደዱ ነው፡፡ መንግስት ይህኛውን ሳይሆን በሱዳን፣ ኬንያና ሶማሊያ የሚፈልሱትን ነው ለማቆም እጥራለሁ የሚለን፡፡ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ ጀኔራሎች የሚሰደዱበትን አብሮ ማንሳት ፖለቲካዊ ቃና ስለሚይዝ ማንሳት አልፈለገም፡፡ 
እርግጥ ነው ወንድምና እህቶቻችን ኮንተይነር ውስጥ መሞታቸው ልብ የሚነካ ነው፡፡ የአሳ ራት፣ የበርሃ ሲሳይ ሲሆኑም እጅጉን ያስቆጫል፡፡ በማያውቁት አገር ፖሊስ ሲገረፉ፣ ሲደፈሩና ሲንገላቱ መስማት ያሳምማል፡፡ መፍትሄም ያስፈልገዋል፡፡ ግን ግን ማዕከላዊ (የኢትዮጵያዊ ጓንታናሞ)፣ የቀጨኔው ወረዳ ዘጠኝ፣ ዝዋይ ታጉረው የሚገረፉት፣ የሚሰቃዩት ዜጎች በስደት ከሚሰቃዩት በምን ይሻላሉ? ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት ሰባት፣ ተቃዋሚ፣አክራሪ…… እየተባሉ የሚገረፉት፣ ከስራ የሚባረሩት የተወለዱበትን አገር ጥለው ሲጠፉ ተጠያቂው ማን ነው? ለምን ለዚህኛው ባይተዋርነትስ አወጅ አይወጣለትም?

የአገራችን ዋነኛው የስደት መንስኤ ፖለቲካዊ ጉዳይ ሆኖ እያለ መንግስት ግን ችግሩን ወደ ደላላ ዝቅ አድርጎታል፡፡ እውነቱን ለመናገር ለኢትዮጵያውያን የስደት ስቃይ መጠየቅ ካለበት ለፖለቲካ ምስቅልቅሉ መንስኤ የሆነው መንግስት ራሱ ነው፡፡

እውቅ ጋዜጠኞች፣ ምሁራን፣ ፖለቲከኞች፣ ጀኔራሎች ወደ ውጭ የሚሰደዱት የቀን ስራ ለመስራት ሳይሆን ልክ ወደ አረብ አገር የሚሰደዴት እህቶቻችን የመን ላይ እንደሚገጥማቸው እስራትና ግርፋት እትብታቸው በተቀበረበት ምድር ስቃዩ ስለበዛባቸው ነው፡፡ አሁንም ቢሆን ስፍር ቁጥር የሌላቸው ዜጎች የዚህ ስቃይ ሰለባዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ወገኖች መውጫ ቀዳዳውን ካገኙ አሁንም ይሰደዳሉ፡፡ ለአንድ ማህበረሰብ ቁልፍ የሆኑት ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች፣ ሙዚቀኞች… በፖለቲካ ችግር ከተሰደዱ ተራው ዜጋም የትውልድ አገሩን የነጠቁትን ሽሽት መጉረፉን ይቀጥላል፡፡ እኛ አገርም እየሆነ የሚገኘው ይኸው ነው፡፡

Friday, October 25, 2013

አዲሱ የወያኔ ስልጣን...አቶ ሃ/ማርያም እገዛ ያስፈልጋቸዋል ከ3 ምክትል ጠቅላይ ሚንስትርነት ወደ አራት ተጨማሪ ረዳትነት ከስራቸው ገብቶላቸዋል

Thursday, October 24, 2013

ወያኔና አሸባሪነት ምንና ምን ናቸው

የወያኔ ጉጅሌ ሰሞኑን የሚያሳዝን ባይሆን ኖሮ በእጅጉ ሊያስቅ የሚችል ቧልት ላይ ተጠምዷል። የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ሳይቀር ህብረተሰቡን በየተቋሙና በየመኖሪያው እየሰበሰበ ስለሽብርተኝነት ማብራሪያና ገለፃ በመስጠት ዜማ ላይ ተጠምዷል።

የወያኔ የሽብረተኝነት ገለፃ ዘመቻ ሚስጥር ደግሞ ብዙ ምርምር የሚሻ አይደለም። የሀገራችን ሰዎች ዶሮ ጭራ ልታወጣው የምትችል የሚሉት አይነት ሚስጥር ነው። አላማው ነጻነት አማረኝ፣ እምቢ ዘረኝነት እና ቢያንስ መሰረታዊ ሰበአዊ መብቴ ይገባኛል በማለት መብቱን እየጠየቀ የመጣው ህዝብ ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ ታይቶታል።

የማእበሉ የመጀመሪያ ንቅናቄዎች ከወዲያ ወዲህ መታየት ጀምረዋል። የገለፀው ሽርጉድ ዋና አላማ ይህ መብቱን የሚጠይቅና አጎንብሶ መኖር የሰለቸው ህዝብ ለመብቴ የማደርገውን ትግል ሽብርተኛ ያስብለኛል ብሎ እንዲፈራና ይበልጥ እንዲያጎነብስ መሆኑ ነው። ይህን ደግሞ ህዝቡ አውቆታል። ሰሞኑን በአለምያ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ለገለፃው ለመጡ ካድሬዎች የሰጧቸው አጸፋዊ ገለጻ ይህንኑ ያሳያል፡፡

ሽብርተኝነት አንድና በነጻነትና በዴሞክራሲ ለመኖር የሚመኝና የወሰነን ህዝብ ሰላም በመንሳት የፖለቲካ አላማዪን አሳካለሁ ብለው የሚያምኑ ቡድኖችና ድርጅቶች የፖለቲካ መሳሪያ ነው። የወያኔ መሪዎች የሽብርተኝነት ትርጉም አልገባቸው ከሆነ ሰብስብ ብለው መሰዋእት ፊት ቢቆሙ ሽብረተኝነትን አፍጥጦ ሊያዩት ይችላሉ፡፡ ሽብርተኛው ወያኔና ወያኔ ብቻ ነው።

ህዝቡ ፊት በቆሙ ቁጥር ግን ህዝቡ ሽብርተኞችን ያያል። ሰለባውን ለማስተማር መሞከር ለእናት ምጥ የማስተማር ያህል ነው፡፡ በኢትዮጵያ ምድር ሁሉንም የዲሞክራሲና የሰላም ጥያቄ ሁሉ በጉልበትና ባፈና የደፈጠጠ አሸባሪ ቁጥር አንድ ወያኔ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ ከሽብር ጋር የመረረ ችግር ላለባቸው ሀገሮች ሎሌነት ገብቶ ሌሎች ሽብርተኞችን ወደሀገራችን የሚጎትተው ራሱ ወያኔ ነው።

ዛሬ በማንም የባእድ አሸባሪ በህዝባችን ላይ ለሚደርስ ጉዳት ዋናው ተጠያቂ ወያኔ የሚሆነውም ለዚህ ነው። ለምእራብያውያን ጸረ ሽብር አጋራችሁ ነኝ እያልኩ ራሴ በምገዛው ህዝብ ላይ የምፈጽመውን ሽብር እንዳለ ያዩልኛል፣ ፍርፋሬም አገኝበታለሁ በሚል ስሌት የተገባበት መሆኑንም የማያውቅ ኢትዮጵያዊ ቁጥሩ ትንሽ ነው።

የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፡- ነጻነት የናፈቀህ፣ አጎንብሶና በገዛ ሀገርህ ተዋርዶ መኖር የሰለቸህ፣ በወያኔ ተሰደህ በባእድ ሀገር የምትሰቃይ፣ የምትሞት የኢትዮጵያ ልጅ ሁሉ ወያኔዎች ከግፍ አልፈው ሊቀልዱብህ፣ በቁምህ ሊገሉህ፣ ሊከፋፍሉህ አይገባም። ወያኔ የፈሪ አብራሪ ነው። አሻፈረኝ ሲሉት እንጂ ቢሸሹለት በቃኝ ብሎ አይመለስም፡፡

ግንቦት 7 ንቅናቄ እንደሁልግዜው ዛሬም ወገን ሆይ፡- የሀገርህን ህልውና ለመታደግ ተነሳ፣ ተቀላቀለን፤ የመከራችንን ቀን አጭር እንደርገው ዘንድ ጸሃይ ሳትገባብን፣ ሳይመሽብን ኑ ተቀላቀሉን የሚለውን ጥሪ ዛሬም አጠናክሮ ያቀርብልሃል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Wednesday, October 23, 2013

በቅርቡ ከኢትዮጲያ ኦጋዴን/ሶማሌ ክልል በድብቅ ወጥቶ በስዊዲን ቴሌቪዥን የተላለፈው ዶክመንተሪ ፊልም የዓለም ህብረተሰብን ያስደነገጠና ያስቆጣ በመሆን የወያኔን አረመኔአዊ አገዛዝ በድጋሚ አጋልጧል ።
ይህ ሁኔታ በጉራፈርዳ ፣ በቤንሻንጉል ፣ በአሶሳ ፣ በወልቃይት ፣ በኦሮሞ ፣ በአማራ ህዝብ እንዲሁም በመላ ዜጎች ላይ እየተፈፀመ ያለውን የጅምላ ጭፍጨፋ አጉልቶ አሳይቶል ።
በመሆኑም የዓለም አቀፍ ሕግ ኮሚሽን ኮሚሽነርና የሕግ ጠበቃ Jurist Stellan Gärde ወያኔ በአለም አቀፍ ፍርድ ቤት ስለሚቀርብበት አግባቦችና ቅድመ ዝግጅቶች ላይ ለኢትዮጲያዊያን ማብራሪያ በመስጠት ተዛማጅ መረጃዎችንም ለማጠናቀር በስብሰባው ላይ ይገኛሉ ።
በተጨማሪም በወያኔ እስር ቤት የተሰቃዩት ማርቲን ሸቤ ስላሳለፉት መከራና በዚሁ ዙሪያ የፃፉትን መፀሃፍ ይዘው በመቅረብ ማብራሪያ ይሰጣሉ ።
ዶክተር ሙሉዓለም አዳም በኖርዌይ የፖለቲካ አክቲቪስት ፣ መቶ አለቃ አበረ አዳሙ በኢትዮጵያ ፖሊስ በኃላፊነቶች የሠሩና የኢ.ፒ.ፒ.ኤፍ (EPPF) መሥራችና የአመራር አባል የነበሩ፣ ጋዜጠኛ ወንድማገኝ ጋሹ የኢሳት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ አዘጋጅ የሰብዓዊ መብት ጥሰትን በተመለከተ በቪዲዮ የተደገፈ ማብራሪያ ያቀርባሉ ።
አዘጋጅ የኢትዮጲያ ዴሞክራሲያዊ መድረክ
በዚህ ውይይት የኢትዮጲያ ጉዳይ የሚያሳስበው ዜጋና የኢትዮጲያ ወዳጆች በሙሉ እንዲገኙ የከበረ ጥሪ እናቀርባለን ።
የሃገር በባህል ምግብ ቡናና ሻይ ተዘጋጅቷል ቀን ኖቬምበር 2- 2013 ዓ .ም ቦታ Stockholm, HallundaFolketshus ሰዓት ከቀኑ 13.00 ጀምሮ .
Sweden
ኢትዮጲያ ለዘላለም ትኑር !!
Image
***ህወሓት/ኢህአዴግ የፈጠራ ውጤቶች***

ህወሓት/ኢህአዴግ ቡድን የኢትዮጵያን ታሪክ መካድ አሳፋሪ በሆነ መልኩ ማቅረብ ታሪክን መበረዝ የፈጠራ ታሪክ መፍጠር:: የኢትዮጵያን ህዝብ ባህል ስብእና ዕምነት ኩራት ማንነት ብሄራዊ እሴቱን አንድነቱንና ብሄራዊ መገለጫዎቹን ማጥፋት:: የኢትዮጵያን ታሪክ የወያኔን ታሪክ ብቻ አድርጎ በካድሬዎቹና ለሆዳቸው ባደሩ ተራ ግለሰቦች ገንዘብ ከፍሎ ማፃፍ:: ልክ እንደ ውጭ ጠላቶቻችን ኢትዮጵያዊነትን ማዋረድ: ማጥላላት: ማናናቅና የመሳሰሉትን አስነዋሪ የቅጥረኝነቱን ተግባር ፈፅሙዋል አሁንም እየፈፅመ ይገኛል::
በ acadamia.org ላይ የመንግስት ሽብርተኝነትን እንደዚህ ጽፎታል፡- State terror refers to the use or threat of violence by the state or its agent or supporters, particularly against civilian individuals and population, as a means of political intimidation and control.
የፖለቲካ የበላይነትን ለመያዝና ጫናን ለመፍጠር በተለይም በሰላማዊ ግለሰቦችና ህዝቦች ላይ ተገቢ ያልሆነን ጥቃትን በራሱ በመንግስት፣ በተወካዮቹና በደጋፊዎቹ ሲፈጸም ይህንን ጥቃት መንግስታዊ ሽብር ብሎታል።
እንግዲህ ህወሓት/ኢህአዴግ ምንም እንካን የመንግስትን ሥልጣን የያዘ ቢሆንም ሌሎች አሸባሪ ድርጅቶች የሚፈጽማቸውን ተግባራት በግልጽና በአደባባይ ይፈጽማል። ከነዚህም ውስጥ ፍንዳታን ይፈጽማል ፣ያፍናል፣ህጋዊ ያልሆኑ እስራትን ይፈጽማል፣በሰብዓዊ ፍጥረት ላይ የማይፈጸሙ ድብደባዎችን፣ በወንዶችም ሆነ በሴቶች የመራቢያ ብልቶች ላይ አደጋን ማድረስ፣አካለ ስንኩል ማድረግ፣ ቤተሰቦች እንዲለያዩ ማድረግ፣ ስውርና የአደባባይ ላይ ግድያዎችንና ሌሎችም ተግባሮችን ይፈጽማል።ከዚህም ድርጊቱ አንጽር ህወሓት/ኢህአዴግ ከአሸባሪነት መገለጫዎች የዘለሉ ተግባሮችን የሚፈጽም ቡድን መሆኑን ያሳያል።
ህወሓት/ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚፈጽመውን የሽብር ጥቃቶችን ኢትዮጵያውያን በግልጽ የሚያውቁት ጉዳይ መሆኑ ፣የልዩ ልዩ ሃገራት መንግስታትና በኢትዮጵያ የሚኖሩ የልዩ ልዩ ሃገራት አምባሳደሮችም ሳይቅሩ በግልጽ የሚያውቁት መሆኑና ይህንንም የሚያግዙ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ መሆናቸው፤በተለይም የዩ.ኤስ.ኤ አሜሪካንና ሌሎችንም መረጃዎችን በመሰብሰብ እና በማጋለጥ የሚታወቀው ዊኪሊክስ ይፋ ባደረጋቸው መረጃዎች መሰረት እነዚህ እውነታዎች ግልጽ እየሆኑ መምጣታቸውና በተለይም ህወሓት የራሱን የሽብርን ጥቃት ለመፈጸም እንዲያግዘው ኢትዮጵያ ውስጥ የሽብር ጥቃት እንዳለ ለማስመሰል ሲጠቀምባቸው የነበሩትን የማታለያ እንቅስቃሴዎች ማለትም የሽብር መሳሪያዎችን በራሱ ወታደሮችና የደህንነት ሰዎች በልዩ ልዩ ቦታዎች በማስቀመጥ መልሶ በራሱ የደህንነት ሰዎች እንደተገኙ በማስመሰል ያደርገዉ የነበረውን ተግባር አጋልጧል፤ እነዚህም ድርጊቶቹ አስቀድሞም ብዙዎች የነበራቸውን ጥርጣሬም አጠናክሮታል።
እውነታው ይህ ነው።

የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዎይ በላምፔዱሳ ህይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን ዘክሮ ዋለ

የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዎይ በላምፔዱሳ ህይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን ዘክሮ ዋለ

የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዎይ በቅርቡ በላምፔዱሳ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን በኦክቶበር 20፥2013 የሻማ ማብራት ፕርግራም በማዘጋጀት ዝክሮ ዋለ፥፥ በዝግጅቱ ላይ ከተለያዩ የሃይማኖት ድርጅቶች፥ ሲቪክ ማህበራት እና የተለያዩ አክቲቪስቶች የስደት መንስኤውንና መፍትሄውን በዝርዝር በእለቱ ለተገኙት ታዳሚዎች መልክት አስተላልፈዋል፥፥
ዝግጅቱን የኢትዮጵያ ማህበር በኖርዎይ ሊቀመንበር አቶ ፋሲል አለባቸው በለቱ የተገኙትን ታዳሚዎች የተደረገውን ጥሪ አክብረው በመምጣታቸው ያላቸውን ምስጋና በራሳቸውን በማህበሩ ስም ካቀረቡ በኋላ የስደትን ህይዎት አስከፊነትና የታሰበለት ቦታ ለመድረስ ምን ያህል አስቸጋሪ እንደሆነና በከፋ መልኩም ህይወትን እስከማጣት እንደሚያደርስ ከገለፁ በኋላ በቅርቡ በላምፔዱሳ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች እግዚአብሄር ነፍሳቸውን እንዲምርና ለቤተሰቦቻቸውም መፅናናትን ተመኝተዋል፥፥
በመቀጠልም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ በተክርስቲያን ቀሲስ ካሳዬ ስደት እና አስከፊነቱን በተመለከተ አጠር ያለ መንፈሳዊ መልክት ያስተላለፉ ሲሆን እንዲሁም ከሙስሊሙ ማህበረሰብ አቶ አያሌው ይመር አጠር ያለ መንፈሳዊ ገለፃ ካደረጉ በኋላ የሰው ልጅ በተፈጥሮ ያገኘውን የመናገር፥ የመፃፍ እና የመደራጀት መብት የመረጠውን ሃይማኖት በሚፈልጋቸው የሃይማኖት መሪዎች እንዳይመራ አምባገነኑ የወያኔ ስርአት በመንፈጉ የኢትዮጵያ ሙስሊምና ክርስቲያን ወገኖች ስደትን እንደ አማራጭ መፍትሄ በመውሰድ በየበረሃውና በየባህሩ ህይወታቸው እያለፈ ይገኛል፥፥ ለዚህም ሁሉ በዜጎች ላይ ለሚደርሰው ጥፋት ዘረኛው የወያኔ ስርአት ተጠያቂ እንደሚሆንና በቅርቡ የሚታዩ ምልክቶች ልክ እንደማንኛውም አምባገነን ስርአት የወያኔ ስርአትም እንደሚገረሰስና የኢትዮጵያ ህዝብም የነፃነትን ድል እንደሚቀናጅ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፥፥ ከዚያም በመቀጠል ከፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ወ/ሮ ሰዋሰው እና ባለቤታቸው ሚስተር ያን ኦገ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ከገለፁ በኋላ ከታዳሚው ጋር በህብረት አጭር የፀሎት ስነስረአት አድርገዋል፥፥
የተለያዩ ፖሊቲካል አክቲቪስቶች ስደት የሚፈጠረው በአንድ ሃገር የአስተዳደር ብልሹነት፥ እንደዜጋ አለመቆጠር፥ የመናገር፥ የመፃፍና የመደራጀት መበቶች ከመነፈግም አልፎ የአንድ ዘር የበላይነት በሃገሪቷ ላይ ስለሰፈነ ዜጎች ስደትን እንደአማራጭ ይወስዳሉ፥ ሆኖም ግን ስደት አማራጭ ይሁን እንጂ ለስደት መንስዔ የሆነው የወያኔ ስርአት የሚወገድበትን መንገድ ባንድነት ተባብሮ መስራት ሲቻል እንደሆነ አስገንዝበው ለዚህም አማራጩ መደራጀትና ባሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገር እየተደረገ ያለውን ከሰላማዊ ትግል አንስቶ እስከ ትጥቅ ትግል የሚያረጉ ሃይሎችን መደገፋና ትግሉን በመቀላቀል እንደሆነ አስገንዝበዋል፥፥
በየፕሮግራሙ መሃል ላይ አርቲት እንዳለ ጌታነህ ያቀረበው ወቅታዊ የሆነ መዝሙርና ስነ ግጥም በለቱ የተገኙትን ታዳሚዎች በእንባ ሲያራጭ አምሽቷል፥፥
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዎይ ይህን የሻማ ማብራት ፕሮግራም ላዘጋጁትና ዝግጅቱም የተሳካ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፆ ላረጉት ለአቶ ዳንኤል አምዶም ፥ ለወ/ት ሳራ ግርማ፥ ወ/ት ለምለም አንዳርጌ፥ አቶ ዮናስ ታምሩ፥ አቶ ሚሊዮን ሊማ፥ አቶ ጌታቸው አበበ፥ እና አቶ ሃሰን ሞሃመድ ታላቅ ምስጋና ያቀርባል፥፥

የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዎይ
ኦክቶበር 22፥2013

Tuesday, October 22, 2013

Candle lighting for the victims of refugees in Lampedusa in italia

አገራችን ኢትዮጵያ በዘረኛው ወያኔ አገዛዝ ከወደቀችበት ጊዜ አንስቶ የዜጎች እንግልት፣
እስራት የጠናጥል እና የጅምላ ግድያ ያልደረሰበት የማህበረሰብ ክፍል ማግኝት አይቻልም::
የመናገር እና የመደራጀት ተፈጥሯዌ መብታችንን ሆኖ ሳለ ዘረኛ ወያኔ ግን ይህንን የተፈጥሮ
መብታችንን በመገፋት ከጊዜ ወደ ጊዜ በሚደርስብን የአፓርታይድ ቅርጽ ያለው አገዛዝ
በመማረር ስደትን እንደ አማራች በመወሰን በየበረሃው ና በየባህሩ ሰምጠው የተቀሩት
ኢትዮጵያኖችን ቤታቸው ና አምጠው የወለዱ እናቶች ይቁጠሯቸው::
አገር ቤት ያሉ ወገኖቻችንን ላይ በሚገርም ሁኔታ የወያኔ ጭቃኔ፣ስቃይ፣እንግልት፣እስር፣
ድብደባ እና ሞት እለት ከእለት የሚሰቃዮ ኢትዮጵያኖች ጥቄቾች አደሉም:: በሌላ በኩል
ደግሞ የሃገራችን ሐብት ና ንብረት በወያኔ ቡድን ተቆጣጥረው ና ለራሳቸው ብቻ በመጠቀም
ይገኛሉ::
አሸባሪ ና ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ ሃገራችንን ኢትዮጵያን ና ህዝባችን ላለፍት 22 አመታት
በጠመንጃ ና ህዝባችንን በመግደል፣በማሰር፣ በማሰዳድ ብሎም ከሃገራቸው ና ከንብረታቸው
ዜጎችን በማፈናቀል በገዛ ሃገራቸው ስደተኛ በማድረግ ገዝቷል አሁንም እየገዛ ይግኛል::
ሰለሆነም ይህ አሸባሪ ቡድን ከሃገራችን ና ከ ህዝባችን እንዲወድቅ ሁሉም ማህበረስብ
በሚችለው ሁሉ ወያኔን ለመጣል በማነኛውም ሁኔታ መታገል አለብን::
ወያኔንን የምንታገለው የወያኔ አላማ ና አጀንዳ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚሰራ ድርጅት
ሰለሆነ ነው:: ኢትዮጵያን ና ኢትዮጵያዊነትን ከመነሻው በጠላትነት ፈርጆ ህዝቧን ና ታሪኳን
እያጠፋ ስለሚገኝ ይንን አሸባሪ የወያኔ አገዛዝ ማስወገድ የእያንዳንዳችን ድርሻ ነው:: ይህም
የሚሆነው ሁሉም ነጻነት ፈላጊ ሁሉ ለነጻነት፣ለዲሞክራሴ ና ለኢትዮጵያ አንድነት የሚታገሉ
ድርጅቶችን መደገፍ የውድ ግዲታ ሴሆን ብቻ ነው:: በተጨማሪም የወያኔን አገዛዝ ና
ጀሌዎችን ለማስወገድ ፊት ለፊት በሃይል ለመጣል ከወሰኑ ሃይሎች አንስቶ አገር ቤት ውስጥ
በሰላማዊ መንገድ በመታገል ያሉትን ወገኖቻችንን የምናደርገው ድጋፍ የበለጠ አጠናቅረን
መቀጠል የሁሉም ኢትዮጵያዊ ግዲታ ነው::
ድል ለ ኢትዮጵያ ህዝብ
ሞት ለወያኔ ና ለሆዳሞች

Friday, October 18, 2013

ወያኔና አሸባሪነት ምንና ምን ናቸው

ወያኔና አሸባሪነት ምንና ምን ናቸው

የወያኔ ጉጅሌ ሰሞኑን የሚያሳዝን ባይሆን ኖሮ በእጅጉ ሊያስቅ የሚችል ቧልት ላይ ተጠምዷል። የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ሳይቀር ህብረተሰቡን በየተቋሙና በየመኖሪያው እየሰበሰበ ስለሽብርተኝነት ማብራሪያና ገለፃ በመስጠት ዜማ ላይ ተጠምዷል።
የወያኔ የሽብረተኝነት ገለፃ ዘመቻ ሚስጥር ደግሞ ብዙ ምርምር የሚሻ አይደለም። የሀገራችን ሰዎች ዶሮ ጭራ ልታወጣው የምትችል የሚሉት አይነት ሚስጥር ነው። አላማው ነጻነት አማረኝ፣ እምቢ ዘረኝነት እና ቢያንስ መሰረታዊ ሰበአዊ መብቴ ይገባኛል በማለት መብቱን እየጠየቀ የመጣው ህዝብ ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ ታይቶታል።
የማእበሉ የመጀመሪያ ንቅናቄዎች ከወዲያ ወዲህ መታየት ጀምረዋል። የገለፀው ሽርጉድ ዋና አላማ ይህ መብቱን የሚጠይቅና አጎንብሶ መኖር የሰለቸው ህዝብ ለመብቴ የማደርገውን ትግል ሽብርተኛ ያስብለኛል ብሎ እንዲፈራና ይበልጥ እንዲያጎነብስ መሆኑ ነው። ይህን ደግሞ ህዝቡ አውቆታል። ሰሞኑን በአለምያ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ለገለፃው ለመጡ ካድሬዎች የሰጧቸው አጸፋዊ ገለጻ ይህንኑ ያሳያል፡፡
ሽብርተኝነት አንድና በነጻነትና በዴሞክራሲ ለመኖር የሚመኝና የወሰነን ህዝብ ሰላም በመንሳት የፖለቲካ አላማዪን አሳካለሁ ብለው የሚያምኑ ቡድኖችና ድርጅቶች የፖለቲካ መሳሪያ ነው። የወያኔ መሪዎች የሽብርተኝነት ትርጉም አልገባቸው ከሆነ ሰብስብ ብለው መሰዋእት ፊት ቢቆሙ ሽብረተኝነትን አፍጥጦ ሊያዩት ይችላሉ፡፡ ሽብርተኛው ወያኔና ወያኔ ብቻ ነው።
ህዝቡ ፊት በቆሙ ቁጥር ግን ህዝቡ ሽብርተኞችን ያያል። ሰለባውን ለማስተማር መሞከር ለእናት ምጥ የማስተማር ያህል ነው፡፡ በኢትዮጵያ ምድር ሁሉንም የዲሞክራሲና የሰላም ጥያቄ ሁሉ በጉልበትና ባፈና የደፈጠጠ አሸባሪ ቁጥር አንድ ወያኔ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ ከሽብር ጋር የመረረ ችግር ላለባቸው ሀገሮች ሎሌነት ገብቶ ሌሎች ሽብርተኞችን ወደሀገራችን የሚጎትተው ራሱ ወያኔ ነው።
ዛሬ በማንም የባእድ አሸባሪ በህዝባችን ላይ ለሚደርስ ጉዳት ዋናው ተጠያቂ ወያኔ የሚሆነውም ለዚህ ነው። ለምእራብያውያን ጸረ ሽብር አጋራችሁ ነኝ እያልኩ ራሴ በምገዛው ህዝብ ላይ የምፈጽመውን ሽብር እንዳለ ያዩልኛል፣ ፍርፋሬም አገኝበታለሁ በሚል ስሌት የተገባበት መሆኑንም የማያውቅ ኢትዮጵያዊ ቁጥሩ ትንሽ ነው።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፡- ነጻነት የናፈቀህ፣ አጎንብሶና በገዛ ሀገርህ ተዋርዶ መኖር የሰለቸህ፣ በወያኔ ተሰደህ በባእድ ሀገር የምትሰቃይ፣ የምትሞት የኢትዮጵያ ልጅ ሁሉ ወያኔዎች ከግፍ አልፈው ሊቀልዱብህ፣ በቁምህ ሊገሉህ፣ ሊከፋፍሉህ አይገባም። ወያኔ የፈሪ አብራሪ ነው። አሻፈረኝ ሲሉት እንጂ ቢሸሹለት በቃኝ ብሎ አይመለስም፡፡
ግንቦት 7 ንቅናቄ እንደሁልግዜው ዛሬም ወገን ሆይ፡- የሀገርህን ህልውና ለመታደግ ተነሳ፣ ተቀላቀለን፤ የመከራችንን ቀን አጭር እንደርገው ዘንድ ጸሃይ ሳትገባብን፣ ሳይመሽብን ኑ ተቀላቀሉን የሚለውን ጥሪ ዛሬም አጠናክሮ ያቀርብልሃል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Thursday, October 17, 2013

" ጊምቢና መንዲ ላይ የምእመናን ልጆች ትምህርት ቤት ውስጥ በፖሊስ ማተባችሁን በጥሱ እየተባሉ ነው"

የመንበረ ፓትርያርክ 32ኛው ጉባኤ የረቡዕ ዕለት ከሰዓት ውሎ ካለፉት የተለየ ነበር፡፡ ዋና አጀንዳው ‹መቻቻልን› የተመለከተ ሲሆን አቅራቢዎቹም ከፌዴራል ጉዳዮች የተወከሉ አካላት መሆናቸውን በዕለቱ የመርሐ ግብር ዝርዝር ላይ ተገልጧል፡፡ ከሰኞ ጀምሮ ይቀርብ በነበረው የአህጉረ ስብከት ሪፖርቶች ላይ የመብት ጥሰትና ሥልጣንን ለግል ሃይማኖት ማስፋፊያ የመጠቀም አዝማሚያዎች መኖራቸውን፣ በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጠው እምነትን የመያዝ፣ የማስፋፋትና የአምልኮ ቦታ የማግኘት መብት እየተጣሰ መሆኑን የሚገልጡ ዘገባዎች ይሰሙ ነበር፡፡

ትናንትናው የከሰዓት ውሎ ስለ መቻቻል ገለጣ ከተሰጠ በኋላ ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳትና የጉባኤው ተሰብሳቢዎች የየአካባቢያቸውን ችግሮች በዝርዝር ነበር ያነሷቸው፡፡ ‹‹መቻቻል እስከ ምን ድረስ ነው›› ብለው ነበር ብጹዕ አቡነ ቄርሎስ የጠየቁት፡፡ ‹‹አሁን በምዕራብ ወለጋ ያለው ሁኔታ መንግሥት በአገሩ ያለ ይመስላል ወይ? ሰው እግሩን እሳት እየበላው ቻል ይባላል እንዴ? እንድንቻቻል አድርጉን፣ እንችላለን›› ነበር ያሉት፡፡
የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ሄኖክ ‹በነጆ ወረዳ በሕጋዊ መንገድ ተሠርቶ የነበረው ቤተ ክርስቲያን በአካባቢው ባለ ሥልጣናት ተጽዕኖ እንዲፈርስ መደረጉን፣ ለምን ታፈርሳላችሁ ብለው ድርጊቱን የተቃወሙ ስድሳ ምእመናን መታሠራቸውን›› በኀዘን ነበር የገለጡት፡፡ አያይዘውም ‹‹በባኮ ወረዳ የተመደቡ አንድ ካህን እያረሱ እያሉ የአካባቢው ባለ ሥልጣናት መጡ፤ ካህኑን በሰደፍ እየደበደቡ ‹ከዚህ ሀገር ልቀቁ፣ ይህ የነፍጠኛ መኖሪያ አይደለም› እያሉ አሰቃዩዋቸው፡፡ ካህኑን ሲደበድቧቸው አንበርክከው፣ ለ15 ደቂቃ አተኩረው ፀሐይዋን እንዲያዩ እያስገደዱ ነበር፡፡ ድብደባውን ሰምተው የወጡት ባለቤታቸው በድንጋጤ ታመው ከጥቂት ቀናት በኋላ ሕይወታቸው አለፈ››
‹‹በሰንበትና በቅዱስ ሚካኤል ቀን ምእመናን ሊያስቀድሱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄዱ ‹ለቅዳሴ ካህናቱ ይበቃሉ፤ እናንተ ውጡ›› እየተባሉ እንዳያስቀድሱ ይደረጋሉ፡፡ ከእኛ ቤተ ክርስቲያን 70 ሜትር ርቀት ላይ ሆን ተብሎ እርስ በርስ ለማጋጨት ለፕሮቴስታንቶች የጸሎት ቦታ ተሰጠ፡፡ ለምን ታጨቃጭቁናላችሁ፤ ይህ ቦታ ለእነርሱ አይሆንም ብሎ በመከራከሩ አንድ ዲያቆን ተደብድቦ ሞተ፡፡ የሕክምና ውጤቱም ሆን ተብሎ በወባ በሽታ ሞተ ተብሎ ተሠራ፡፡ ለሁለት ዓመት ያህል ተከራክረን አሁን ቦታው ለእኛ ተወሰነ፡፡
ጊምቢና መንዲ ላይ የምእመናን ልጆች ትምህርት ቤት ውስጥ በፖሊስ ማተባችሁን በጥሱ እየተባሉ ነው፡፡ ለምን ስንላቸው ከላይ የወረደ መመሪያ አለ ይሉናል፡፡››
ቀጥለው የሀገረ ስብከታቸውን ችግር ያቀረቡት የጋሞጎፋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤልያስ ነበሩ፡፡ ‹‹በጋሞ ጎፋ መቱ ወረዳ፣ ዋጁ ኡቆ ላይ የመስቀል ማክበሪያ ቦታችን ለሱቅ መሥሪያ ቦታ ተሰጠ፡፡ አቤት ብንል የሚሰማን በማጣታችን ዘንድሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ መስቀል ሳናከብር ዋልን፡፡ ሀገሪቱ በችግር ላይ በነበረች ጊዜ እንኳን መስቀል ሳይከበር ቀርቶ አያውቅም ነበር፡፡ የቤተ ክርስቲያን የይዞታ ቦታ ለመንግሥት እየተሰጠ ነው፡፡ በአቡነ ጳውሎስ ዘመን በቅዱስነታቸው በኩል ለክልሉ ደብዳቤ ጻፍን፡፡ ክልሉ ወሰነልን፡፡ ነገር ግን እስካሁን አልተረከብንም፡፡››
ቀጥለው ሃሳባቸውን የሰጡት የባሰ ካልመጣ በቀር ድምጻቸው ማይሰማው ብጹዕ አቡነ ያሬድ የሶማሌ ክልል ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ነበሩ፡፡ ‹‹በሶማሌ ክልል አምስት አብያተ ክርስቲያናት ብቻ ናቸው ያሉን፡፡ ምእመናኑ ብዙ ናቸው፡፡ ሲወልዱ የሚያስጠምቁበት፣ ሲያርፉ የሚቀበሩበት ቤተ ክርስቲያን እንትከል ብንል የሚሰማን አጥተናል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን የሚረዱ ምእመናን በግላቸው ጥቃት እየደረሰባቸው ነው፡፡ ለዚህ መልሳችሁ ምንድን ነው›› ብለዋል፡፡
በገለጻው ላይ ኢትዮጵያ ክርስትናን የተቀበለችው በ4ኛው መክዘ ነው የሚለውን የተቃወሙት ብጹዕ አቡነ ማርቆስ ‹‹ታሪክ ክፉም ሆነ በጎ እንደ ታሪክነቱ መተረክ አለበት፤ አቅራቢው ወንድማችን በ4ኛው መክዘ ክርስትና ገባ ያልከው ተሳስተሃል፡፡ ለመሆኑ ይህንን ለማለት ‹ላይሰንስ አለህ?› አባቱን የሚኮንን ልጅ ምን ያደርጋል? ነገሥታቱን ወቀሳችሁ፣ ቤተ ክርስቲያንን ነቀፋችሁ፤ ለመሆኑ ከማን ነው ይህቺን ሀገር የተረከባችሁት? ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ የገባው ጌታ ባረገ ዓመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 8 ላይ አለ፡፡ ይህንን ዛሬ ‹ግራጁዌት አድርገው›፤ ልዑካኑ ስትመጡ ስለምትናገሩት ነገር ዕወቁ፤››
የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ እንድርያስም ‹‹በቤተ መንግሥት የወርቅ ዕቃ ብቻ አይኖርም፣ የእንጨትም፣ የድንጋይም ዕቃ አለ፡፡ በቤተ ክርስቲያንም ሁሉም ጥሩ አይሆንም፣ መጥፎም ይኖራል፡፡ ነገር ግን እስከ መጨረሻው የጸና ይድናል ብሏል፡፡ በእኔ ሀገረ ስብከት ስድስት አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፡፡ ሦስቱ በአንድ አካባቢ፣ ሦስቱ በሌላ ቦታ፡፡ ይህንን ለክልሉ መንግሥት ብናሳውቅ አልረዱንም፡፡ የተበደለ ሰው ይጮኻል፤ ሲጮህ ደግሞ ፖለቲካ ነው ይባላል፡፡ ድሮ ያስቸገረን የንዋያተ ቅድሳት ዘረፋ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ቤተ ክርስቲያን ወደ ማቃጠል ተዛውሯል፡፡ አንዱ ባለ ሥልጣን እንዲያውም ችግሩን ሳቀርብለት ተቆጣኝ፤ ብዙ ብናገር ነፋስ ስለሚወስደው እዚህ ላይ ይብቃ››
ከብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳት ቀጥሎ የተናገሩት የወላይታ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ‹‹በበዴሳ ወረዳ ያለ አንድ የሌላ እመነት ተከታይ የሆነ ዳኛ ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጋር ቄራ አንካፈልም፤ በመኪና አብረን አንሄድም› ብሎ ዐወጀ፡፡ በጋራ በመቻቻል የኖርንበትን ዕድር ሁሉ ለዩ ብሏል፡፡ ታድያ እንዴት መቻቻል ሊመጣ ይችላል፡፡››
ከጉባኤው የቀረበውን ቅሬታና ሃሳብ ያዳመጡት የፌዴራል ጉዳዮች የሥራ ኃላፊዎች የቀረቡት ቅሬታዎች በሰነድ ተደግፈው ቢደርሷቸው እነርሱም በመፍትሔው ላይ መሥራት እንደሚችሉ፤ ኢትዮጵያ የሃይማኖቶች ጉባኤም ጉዳዩ በየደረጃው ቢቀርብለት መፍታት እንደሚችል፡፡ ቅሬታዎችን እንደዚህ ባለ መድረክ ከሚሆን በየጊዜው እየተገናኙ መፍታት ቢቻል›. የሚሉ ሃሳቦችን ሠንዝረዋል፡፡
የዘንድሮው የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ በአደረጃጀቱ ውበት፣ በተሳታፊዎቹ ብዛት፣ በአህጉረ ስብከቶች ቁጥር(50 ደርሰዋል)፣ በስብሰባው ቁም ነገረኛነት ካለፉት የተለየ ነበር፡፡ እነ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ የሰበካ ጉባኤ ስብሰባ ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን በብርቱ እንደ ደከሙበት ያሳያል፡፡ በየዘገባዎቹ የተሰሙትን የመብት ጥሰቶች፣ ሥልጣንን ተገን በማድረግ የሚፈጸሙ ጫናዎች፣ የአምልኮ ቦታ እጥረቶች፣ በካህናቱ ላይ የሚፈጸሙትን ግፎችና፣ የቤተ ክርስቲያንን ይዞታ የመንጠቅ ርምጃዎች ግን ሊገቱ ይገባቸዋል፡፡ ከአንዳንድ ክልሎች በቀር በብዙዎቹ የዞንና የክልል ባለ ሥልጣናት ችግሩን ተረድተው ለመፍታት እንደሚጥሩ ተገልጧል፡፡ በወረዳ ደረጃ የሚገኙት ግን ሥልጣንን ተገን በማድረግ የግል እምነታቸውን እያስፋፉ መሆኑን ያሳያል፡፡ በደቡብ ጎንደርና በምሥራቅ ጎጃም የተፈጸሙት የአብያተ ክርስቲያናትን የማቃጠል ርምጃዎች በጊዜው ተጣርተው መፍትሔ ካልተሰጣቸው ፍጻሜያቸው አያምርም፡፡
በየአካባቢው በሚገኙ ባለ ሥልጣናት የሚፈጸሙ ትንኮሳዎችም መቆም አለባቸው፡፡ ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳቱ ‹አታስቆጡን› እያሉ ደጋግመው የተናገሩት ነገር የዋዛ አይደለም፡፡ ኃላፊነት የማይሰማቸው አካላት የሚፈጽሙት ገደብ አልባ ትንኮሳና ጫና ወዴት እያመራ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
ቤተ ክርስቲያኒቱም አደረጃጀቷንና አሠራርዋን ይበልጥ የምትፈትሽበት፣ አሁን ለገጠማት ተግዳሮት ብቁ የሚሆን አሠራና አወቃቀር የምትይዝበት፣ ችግሮችን በስብሰባ ብቻ ሳይሆን በአካባቢያዊ ውይይት፣ በሕግ መሥመርና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ በመሥራት የምትፈታበት መንገድ ሊኖር ይገባል፡፡
ያለበለዚያ መጋቤ ምሥጢር ወልደ ሩፋኤል የተረተው ተረት መድረሱ የማይቀር ነው፡፡
በጣልያን ጊዜ ነው አሉ፡፡ ጎንደር ላይ ጣልያን በድማሚት አንዱን ተራራ ያናውጠዋል፡፡ ተራራው ‹እድም› እያለ ይፈርሳል፡፡ አንዲት የከብት እረኛ ልጅ ፈርታ ወደ እናቷ ሄደችና ‹እማዬ ኧረ ጣልያን ተራራውን እያፈረሰው ነው›› አለቻት፡፡ እናቷም ‹‹እነ ደጃዝማች እገሌ፣ እነ ፊታውራሪ እገሌ፣ እነ ራስ እገሌ እጅ አንሰጥም ብለው እየተጋደሉ ዐለፉ፡፡ ተራራውንስ ተይው ያፍርሰው፤ እርሱም መቀመጡን አብዝቶት ነበረ፡፡›› አለቻት አሉ፡፡

Wednesday, October 16, 2013


የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዌይ በቅርቡ በስደት ላይ ህይወታቸውን በባህር ላይ ያጡትን ውገኖቻችንን ለማሰብ የሻማ ማብራት ዝግጅት ስላምናረግ እሁድ ኦክቶበር 20፥ 2013 ከ16፥00 እስከ 18፥00 ሰዐት በኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት ለወገኖቻችንና ለቤተሰቦቻቸው አጋርነትዎን እንዲያሳዩ ማህበሩ ጥሪ ያቀርባል፥፥

የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዌይ

በዝግጅቱ ላይ የሃይማኖት አባቶችና የተለያዩ እንግዶች ንግግር ያረጋሉ፥

የአስተዳደሩ ምርመራና ክስ ኤክስፐርት በቁጥጥር ሥር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ

-በቦሌ ጉምሩክ ኃላፊና በአንድ ባለሀብት ላይ የተዘጋጀው ክስ ሳይነበብ ቀረ
በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈጸሙት በሥልጣን ያላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው፣ በማረሚያ ቤት በሚገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት
አስተዳደርና ግንባታ ፈቃድ ባለሥልጣን በነበሩት አቶ ቃሲም ፊጤ መዝገብ፣ በሌሉበት ክስ ተመሥርቶባቸው የነበሩት፣ የአስተዳደሩ ፍትሕ ቢሮ የምርመራና ክስ ኤክስፐርት አቶ ተስፋዬ ዘመድኩን በቁጥጥር ሥር ውለው ጥቅምት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡
የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሠረተባቸው አቶ ቃሲም ፊጤ፣ አቶ ተስፋዬ ዘመድኩን፣ የሊዝ አሰባሰብ ክትትል ኦፊሰር አቶ ገብረየሱስ ኪዳኔና የመሬት አቅርቦት አፈጻጸም ንዑስ የሥራ ሒደት አቶ በቀለ ገብሬ መሆናቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ 
ሦስቱ ተከሳሾች ሐምሌ 29 ቀን 2005 ዓ.ም. የተጻፈ ክስ ቀርቦባቸውና ተነቦላቸው የዋስትና መብታቸው በመከልከሉ፣ ማረሚያ ቤት ቆይተው ጥቅምት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ 
ከሦስቱ ተከሳሾች በተጨማሪ በሌሉበት ክስ ተመሥርቶባቸው የነበሩት አቶ ተስፋዬ አብረው በመቅረባቸው ቀደም ብሎ የተመሠረተው ክስ ተነቦላቸዋል፡፡ የዋስትና መብታቸውም ታልፎ በማረሚያ ቤት ሆነው ክሳቸውን እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱ በጽሕፈት ቤት በኩል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ከአቶ ተስፋዬ በስተቀር ሦስቱ ተከሳሾች ለጥቅምት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. ተቀጥረው የነበሩት የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ የቅድመ ክስ መግለጫ እንዲያቀርብ የነበረ ቢሆንም፣ አቶ ተስፋዬ ተይዘው በመቅረባቸው ክሱ እንደ አዲስ ተነቦላቸው በሁሉም ላይ የቅድመ ክስ መግለጫ ለማቅረብና ተከሳሾች በጠየቁት የዋስትና መብት ላይ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡
ሌላው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥቅምት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ ኃላፊዎች፣ ሠራተኞችና ነጋዴዎች ጋር በቁጥጥር ሥር ውለው በነበሩት በባለሥልጣኑ ቀድሞ የቦሌ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዮሴፍ አዳዩና በተለያዩ ንግድ ሥራዎች ላይ የተሰማሩት አቶ ማሞ ኪሮስ ላይ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ክስ አዘጋጅቶ የመጣ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ በእድሳት ላይ በመሆኑ ዳኞች ቀድሞ ይሠሩበት ከነበረው ችሎት ወደ ሌላ ችሎት በመቀያየራቸውና ሳይሟሉ በመቅረታቸው ሳይነበብ ቀርቷል፡፡ 
አቶ ማሞ ኪሮስ ሐሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ተሳትፈዋል በሚል መጠርጠራቸውንና አቶ ዮሴፍ አዳዩ በሥልጣን ያላግባብ መገልገል፣ ፈቃድ የሌለው የጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘትና በሌሎችም ወንጀሎች መጠርጠራቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡


‹‹ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ መሞታቸው ተነግሮናል›› – (አቶ ስብሃት ነጋ)



በኢትዮ – ኤርትራ ጦርነት ወቅት ያበሩት የነበረው የጦር አውሮፕላን ተከስክሶና ቆስለው በሻዕብያ እጅ ለሁለተኛ ጊዜ የወደቁት ጀግናው ኢትዮጵያዊ ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ በኤርትራ እስር ቤቶች በስቃይ ቆይተዋል፡፡
ጦርነቱ አብቅቶ ሁለቱ አገሮች የጦር ምርኮኞቻቸውን ሲቀያየሩ የኢትዮጵያ መንግስት በኮሎኔሉ ጉዳይ ገፍቶ መሄድ ባለመቻሉ በዛብህ ወደ አገራቸው ሳይመለሱ በኤርትራ እስር ቤት መቅረታቸውን የመንግስት ተቃዋሚዎች ይናገራሉ፡፡
የኮሎኔሉ ቤተሰቦች ደህንነታቸውን ይሰሙ የነበሩት ከአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ሰራተኞች የነበረ ቢሆንም ግንኙነቱ መቋረጡን ለአብራሪው ቤተሰቦች ቅርበት ያላቸውና የኮሎኔሉ ወንድም ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ለላይፍ መጽሔት ሰጥተውት በነበረ ቃለ ምልልስ መናገራቸው ይታወሳል፡፡
የኮሎኔሉ ቤተሰቦች በተለያዮ ጊዜያት ወደ መንግስት አቤት በማለት አብራሪውን በዲፕሎማሲ ጥረት ከእስር እንዲያስፈቱ ሲወተውቱ ቢቆዮም መኖር አለመኖራቸውን እንኳን የሚያረጋግጥላቸው እስከማጣት መድረሳቸው ጉዳዮን ለፈጣሪ ከመስጠት የዘለለ አማራጭ እንዳይኖራቸው አድርጓል፡፡
የኢትዮጵያ የሰላምና ልማት ኢንስቲትዮትን የሚመሩት የቀድሞው የህወሃት ነባር ታጋይ አቶ ስብሃት ነጋ አሜሪካን አገር ጎራ ባሉበት አጋጣሚ ከገዛ ፓልቶክ ሩም ተሳታፊ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ‹‹ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ መሞታቸው ተነግሮናል፡፡አሁን እየጠየቅን የምንገኘው ከሞቱም ሬሳቸውን እንዲያሳዮንና የአሟሟታቸውን ምክንያት እንዲነግሩን ነው፡፡››በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡የፓልቶኩ አቅራቢም በኮሎኔሉ ሞት የተሰማትን ሀዘን በፓልቶኩ ስም ገልጻለች፡፡
የስብሃትን ንግግር ተከትሎ የኮሎኔሉ ቤተሰቦች በስብሃት የተነገረውን ከዚህ ቀደም መስማታቸውን ለማረጋገጥ ሞክረናል፡፡ የኮሎኔሉ ቤተሰቦች በዛብህ ሞተዋል ተብለው በይፋ አለመረዳታቸውን ባደረግነው የማጣራት ሙከራ ለማወቅ ችለናል፡፡ ስብሃት ነጋ በኤርትራ 27 የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን የጦር ምርኮኞች እንደሚገኙ በቃለ ምልልሳቸው አስታውቀዋል፡

Sunday, October 13, 2013


በአሌክሳንደሪያ ቨርጂኒያ ከአንድ ሰአት በፊት ስብሃት ነጋና አብሯቸው የነበረ ግለሰብ በአንድ ኢትዮጲያዊ ላይ ከፍተኛ ድብደባ ፈፅመው ማምለጣቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።


Wednesday, October 9, 2013



አቶ ሐ/ደሳለኝ በሟች መለስ ዜናዊ አማካይነት በኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲህ ሲሉ ቀለዱ ....

የተቃዋሚዎች ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ መብታቸው ነው ሕገ መንግስታዊ መብታቸው ነው::ያው የሚጠይቁት ጥያቄም የሚታወቅ ነው አዲስ ጥያቄ አይደለም::ቤት ቁጭ ብሎ መጠየቅና አደባባይ ወቶ መጠየቅ ነው ልዩነቱ ሰለዚህ ሕዝቡም ሰንቷቸዋል ዋናው ጉዳይ ሰልፍ የሚወጣው ሕዝቡን ለማሰማት ይመሰለኛል.... ሕዝቡን አሰምተውታል...ሰለዚህ ዲሞክራሲ ተሳክቷል ማለት ነው .... የዲሞክራሲ ሰርዓት ሂደት ተሳክቷል ማለት ነው ....ድምፃቸውን ማሰማት ሕዝቡን እንዲያውቅ ማድረግ ችለዋል ....ሕገ መንግስቱም የሰጣቸው መብት ሰለሆነ ማንም በችሎታ የሰጣቸው አይደለም...ሰለዚህ ያንን ፈጽመዋል ይሄ ሕገ መንግስታዊ ሕግ ነው::ነገር ግን ምን ምላሽ እንደሚሰጥ አናውቅም ::ይሄ እንግዲህ ከ100 ግዜ በላይ መልስ ሰተናል:: እንግዲህ ጫና ፈጥረን መንግስት ሃሳቡን እንዲቀይር ለማድረግ የሚያስቡ ይመሰለኛል....በሂደት ውስጥ መንግስት ትክክለኛና እውነተኛ ምላሽ መሆን ያለበትን ምላሽ አሰቀድሞ የሰጠ ሰለሆነ አሁን ጫና ፈጥረው የሚቀየር ነገር ብለው የሚያስቡት ነገር ካለ የሚፈጠርም የሚቀየርም ነገር የለም::ሰለዚህ አሰቀድመን የሰጠ መልስ ተከታታይ ነው ......ነገር ግን የሚያሳዝነው ሌት ከቀን ተመሳሳይ ጥያቄ እየያዙ ጥበቃ ሰናካሄድ ተመሳሳይ ጥያቄ እየያዙ ጥበቃ ሰናካሄድ በየ እሁዱ ጥበቃ ስናካሄድ በየ እሁዱ ጥበቃ ሰናካሄድ መሰልቸት ነው የሚሆነው እንጂ ጥያቄው ያው ነው:: አንዱ ሲተው ሌላኛው እኛ አገር 99 ፓርቲ ነው ያለው እንግዲህ 99 እሁድ መጠበቅ አለብን ማለት ነው:: ነገር ግን ዲሞክራሲ ሰለሆነ እንታገሳለን ....የሆነው ሆኖ በጣም ብዙ ሰራ ያሰፈታል......መታወቅ ያለበት አንድ ጥያቄ በተደጋጋሚ የሚጠየቅ ከሆነ እኛም አንድ ቦታ ሰንደርስ ለዚህ ጥያቄ እኮ ብዙ ግዜ መልስ ሰተናል ጥያቄው ይሄ ከሆነ ሰልፍ ምንድነው ትርጉሙ ብለን የምናቆምበት ግዜ እንደርሳለን ማለት ነው ሰልፍ ለዘላለም ዝም ብሎ የሚካድ ያለበት ሃገር ያለ አይመሰለኝም::ሰለዚህ ይሄ መታየት አለበት ::

ሁለተኛው ይሄ ሰልፍ የሚያካሄዱበት ዕቅድ የራሳቸው ዕቅድ አይደለም.... አቅደው የሰጧቸው ከኋላ ባለቤቶቹ አሏቸው:: ባለቤቶቹ ሰልጠና ሰተዋቸው አሜሪካን ወይም ሌላ ሃገር ቁጭ አርገዋቸው አሰልጥነው በዚህ በዚህ ብትሄዱ መንግስተን አጣብቂኝ ውሰጥ ትከታላቹ ሰለዚህ ተከታታይ የሆነ ሰልፍ ለማካሄድ ዕቅድ አውጡ ብለው እራሳቸው አቅደው አሰልጥነው ኦሬንቴሽን ሰተው በዕቅዱ ላይ አሰማርተዋቸዋል......ሰለዚህ የባለቤታቸውን ሰራ እየሰሩ ሰለሆነ ....የራሳቸው ሰራ ስላይደለ በሂደት ያው ባለቤቱም ይሰለቻል እነሱም ሰልችቷቸው የሚያቆሙ ይመሰለኛል:: እኛ ግን እንደመንግሰት ሃላፊነታችን ሕገ መንግስታዊ መብታቸው ሰለሆነ ያንን እንዲያሰተናግዱ ማድረግ ነው :: ከዛ ባሻገር አሁን ምን እናድር ? መንግስት እኛን አልሰማም እናንተ ንገሩልን እያሉ ነው ያቀዱትን አካላት ማለት ነው :: እነዛ ደግሞ አይ እናንተ በቀጥታ የምትሳተፉበት ጉዳይ እንደመሆኑ መጤን እኛ ደግሞ ለመንግስት ሄደን መናገር አንችልም ይልውቸዋል .....ሰለዚህ ሂደቱ እንደዚህ አይነት ደካማ ሂደት ነው ያለው so በኛ በኩል በተደጋጋሚ ምላሽ ሰተናል በተደጋጋሚ ምላሽ የሰጠነው ጉዳይ ሰለሆነ ተጨማሪ የምንሰጠው ምላሽ በዚህ ጉዳይ ላይ የለንም::ብለው ቀልዳቸውን ዘግተዋል ::

ባጭሩ አቶ ሐ/ማርያም ደሳለኝ ያሉት ኢትዮጵያ ውሰጥ እኛን ለመቃወምም ሆነ ያንን የመሰለ ሰልፍ ለማቀናጀት ብቃት ያላቸው ፓርቲዋች የሉም ጭንቅላት የላቸውም አይነት በንቀት የተሞላ ቀልድ ነው የተናዘዙት (እሳቸው እራሳቸው በሙት እየተመሩ እንደሆነ ማን በነገራቸው ያሉሽን ባልሰማሽ ገበያ ባልወጣሽ አለ ሽምሱ) በዚህ አጋጣሚ እሳቸውና መንግስታቸው ለዘላለም እንደሚገዙም ሊነግሩን ሞክረዋል :: 99 ፓርቲ ነው ያለው ላሉት ይሄ ወያኔ ሌ ንቅፍት እውቅና የሰጣቸውም አብረው እንደተቆጠሩ እናውቃለን እኛ አሉ የምንላቸው ወያኔ 5 ለአንድ አድርጎ ፓርቲ ያላቸውን ሳይሆን በተግባር እየሰሩ ያሉትን ብቻ ነው:: የኢትዮጵያ ሕዝብ የተነሳለት ምን ይሉ ይሆን ?


ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!!

Free Esklnder Nega

በቅርብ ወሰ ጣልያን ሲሄዱ ወደ 300 ሰው በባህር ሰምጦ ሲሞት ይህ የምዩት ፎቶ ከዛ ሞት የተረፉት ሰደተኞች ናቸው

ስደት ክፉ ነገር መድረሻው አይታወቅ
ለህፃን ለወጣት ርህራሄ የማያውቅ
ፍታ በማይሰጠው በውሃ እፍንታ
ወገን ተሽነፈ መረጠ እፎይታ !!

መታሰቢያነቱ ሰሞኑን በጣልያን ባህር ላለቁት ሰደተኞች ይሁን !!
Two men who survived the tragedy look on. They were on the boat that travelled for two days from Libya before running into trouble and eventually sinking close to LampedusaSurvivors of the shipwreck look out to sea as the Italian Navy and coast guard carry on searching Two men who survived the tragedy look on                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                   
                                                                                                                                                                                                  
ወጣቶችን የማደኑ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ወጣት ወይንሸት ስለሺ በትላንትናው እለት ከምሽቱ 1፡00 በፖሊስና ደህንነቶች ተይዛ ፖሊስ ጣቢያ በግድ እንድትሔድ ተደረገ

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ መስከረም 19 ቀን 2005 ዓ.ም ባካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ሳቢያ በሰልፉ ላይ የነበሩ ወጣቶችን በተለይም በእለቱ ጎልትው ይታዩ የነበሩ ወጣቶችን ለመያዝ ፖሊስና ደህነት ነን የሚሉ ሲቪል ለባሾች የአደን ስራውን አጠናክረው ቀጥለውበታል በትላንትናው እለት ማለትም በ28/01/2006 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 የአዲስ አበባ ዞን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፀሀፊ የሆነችውን ወጣት ወይንሸት ስለሺን እስታዲዮም አካባቢ ታክስ ለመሳፈር ስትል አንድ የሲቪል ልብስ የለበሰና አንድ የፓሊስ ልብስ የለበሰ ዘገየ የሚል መታወቂያ ካርድ የያዘ ፖሊስ ለምርመራ ትፈለጊያለሽ በማለት ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንድትሔድ ለማስገደድ ቢሞክሩም ‹‹ህጋዊ ዜጋና ቋሚ የመኖሪያ አድራሻ ያለኝ በመሆኑ የመጥሪያ ወረቀት አለበለዚያ የፍርድ ቤት ማዘዣ ሊደርሰኝ ይገባል እንጂ ማንም እንደፈለገ ተከተይኝ ስላለ እንደበግ ተከትዬህ የምሄድ አይደለሁም መብትና ግዴታዬን የማውቅ ዜጋ ነኝ››አልሄድም በማለቷ ግርግር የተፈጠረ ሲሆን በመጨረሻም በሀይል በማስገደድ ቂርቆስ አካባቢ ወደሚገኝ ፓሊስ ጣቢያ እንደወሰዷትና በወረቀት የተፃፈ ስም ዝርዝር በማውጣት ስሟን እንደገለፁላትና ከሚፈለጉት የአንድነት አባላት መካከል እንዷ እንደሆነች እንዲሁም የሰልፉ እለት ቱታ ለብሰው ከነበሩ ወጣቶች መካከል አንዷ መሆኗንና የወንጀለኛ መቅጫ ህጉን የሚፃረር ድርጊት አንቺና ግብርአበሮችሽ ፈፅማችኋል በዚህም አንለቅሽም የሚሉ ማስፈራሪያና ዛቻዎችን ያደርሱባት እንደነበር የገለፀች ሲሆን ያደረግነው ድርጊት በአደባባይ እንጂ በስውር አይደለምና ወንጀል ሆኖ የሚታይ ከሆነ የፈለጋችሁትን እርምጃ መውሰድ ትችላላችሁ የእኛ መሰረት አሁን በስራ ላይ ያለው ህገመንግስት እንጂ ሌላ መመሪያን ወይም ደንብን መሰረት ያደረገ ባለመሆኑ ነገም ሆነ ከነገ ወዲያ ተመሳሳይ የትግል ስትራቴጂዎችን እንጠቀማለን አይሆንም የምትሉ ከሆነ አሁንም እዚሁ የፈለጋችሁትን ማድረግ ትችላላችሁ ፈርቼ ወደኋላ አልመለስም በማለት አቋሟን እንደገለፀችና በዚህም ምክንያት የተለያዩ የስድብና የማስፈራሪያ ቃላቶችን ይጠቀሙ እንደነበር ከዛም ከምሽቱ 3፡00 ላይ መውጣት እንደምትችል ተገልፆላት ከጣቢያው ብትወጣም ትራንስፖርት ማግኘት ባለመቻሏ በጨለማ በእግር ወደቤቷ ለመሄድ መገደዷን ገልፃለች፡፡ወጣት ወይንሸት በ2005 ዓ.ም ግልፅ ደብዳቤ ለከንቲባ ኩማ ደመቅሳ በሚል በፃፈችው የጋዜጣ ፅሁፍ ሳቢያ በደህንነቶች ታፍና በመወሰድ የኤሌክትሪክ ሾክና በዱላ እስከመደብደብ የደረሰ ሰብአዊ መብት ጥሰት እንደተፈፀመባት ይታወቃል፡፡