የመንግስት ካድሬዎች ” የሶማሊ ተማሪዎች ከመንግስት ጎን ቆመው በኦሮሞ ተማሪዎች ዙሪያ መረጃ እየሰጡን ነው” የሚል አሉባልታ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች መነዛቱ፣ የሶማሊ ተማሪዎችን ስጋት ላይ የጣላቸው ሲሆን፣ ተማሪዎቹ ከመንግስት ጎን አለመቆማቸውንና እንዲህ አይነት አሉባልታ እየተነዛ ያለው የሁለቱን ብሄር ህዝቦች ለማጋጨት መሆኑን እየተናገሩ ነው።
የተማሪዎች ወላጆች በሚነዛው ወሬ መደናገጣቸውንም ለማወቅ ተችሎአል።
ጉዳዩን በማስመልከት ጥያቄ ያቀረብንለት የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት አማካሪ የነበረውና የስዊድንን የአንቲገን ሽልማት አሸናፊ የሆነው አብዱላሂ ሁሴን ወሬው እንዲህ አይነቱ አሉባልታ በስፋት የሚሰራጨው የሁለቱን አካባቢዎች ተወላጆችን ለማጋጨት ነው ብሎአል።

No comments:
Post a Comment